ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፣ የቀድሞው የኳታር አሚር ሼይኽ ሀማድ ቢን ካሊፋ አልታኒ ሕልፈትን ተከትሎ የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ለመግለጽና ለቅሶ ለመድረስ ኳታር ዶሃ ገብተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስፍራው በመገኘት፣ ለኳታር ሕዝብና መንግሥት እንዲሁም ለንጉሣዊው ቤተሰብ የአጋርነትና የጽናት መግለጫ መልእክታቸውን ያደርሳሉ።
ሼይኽ ሀማድ ቢን ካሊፋ አልታኒ ኳታርን ወደ ዘመናዊ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ምዕራፍ ያሸጋገሩ ታላቅ መሪ እንደነበሩ ይታወሳል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልዑክ በዶሃ ቆይታው፣ ከሀገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በኢትዮጵያ እና በኳታር የሁለትዮሽ ግንኙነቶች ዙሪያ አጫጭር ውይይቶችን ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
