ጠ/ሚ ዐቢይ ከትግራይ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ጋር ተወያዩ

Date:

ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ከትግራይ የተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ጋር መወያየታቸውን ገልፀዋል።

በውይይቱ በተለይም የተፈናቃዮች ጉዳይ፣ የትግራይ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚዊ ሁኔታዎች ላይ በዋናነት ምክክር የተደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዮች እንደነበሩ ተገልጿል።

በፐብሊክ ዲፕሎማሲው አባላት በኩል በርካታ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን፤ መንግስት ከህዝቡ ጋር ተቀራርቦ መስራት እና ህዝባዊ የውይይት መድረኮችን ማዘጋጀቱን ሊቀጥል ይገባል የሚሉትን ጨምሮ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተዋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰራጩት መልዕክት ገልጸዋል።

በመልዕክቱ፤ በፐብሊክ ዲፕሎማሲው አባላት ሁሉን አቀፍ ብሄራዊ ውይይት እና የትግራይ ህዝብ ድምጽ በትክክል የሚሰማባቸው ክፍት መድረኮች መቋቋም እንዳለባቸው አሳስበዋል ብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...