“ ጨዋታው የሚደረገው ህዳሴ መመረቂያ ላይ በመሆኑ ትልቅ ትርጉም አለው “ አቶ ባህሩ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አርብ ከግብፅ ጋር ያለበትን የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ አስመልክቶ በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን “ ጨዋታው ልዩ ትኩረት የሰጠነው ነው “ ሲሉ ገልጸዋል።

“ ጨዋታው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እንዲሁም የኢትዮጵያ ህዝብም ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ጨዋታ ነው “ ሲሉ አቶ ባህሩ ጥላሁን ተናግረዋል።

አክለውም “ ጨዋታው ትልቅ ታሪካዊ አሻራችንን ያስቀመጥንበት ህዳሴ ግድብ በሚመረቅበት እና ንጋት ሀይቅ በተሰየመበት ሰዓት ስለሆነ የሚደረገው ትልቅ ትኩረት ሰጥተነዋል “ ብለዋል።

“ ቡድኑ የተቻለውን ሁሉ እንዲያደርግ እንፈልጋለን ያንን እንዲያደርግም ነው ቀደም ብሎ ዝግጅት እንዲጀምር ያደረግነው “ አቶ ባህሩ ጥላሁን

የዋልያዎቹ ዋና አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ በበኩላቸው “ ጠንካራ ጨዋታ ነው የሚጠብቀን “ ብለዋል።

“ እኛም በዛው ልክ ተገቢውን ጥሩ ዝግጅት አድርገናል ሜዳ ላይ የሚሆነውን እናያለን “ ሲሉ አሰልጣኙ ተናግረዋል።

@tikvahethsport    

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...