ዳማት ሆቴል እና ቢዝነስ ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በሆቴልና ቱሪዝም፣ በማርኬቲንግ እና ሴልስ ማኔጅመንት፣ አካውንቲንግና ፋይናንስ፣ በማኔጅመንት፣ በኢንሹራንስ ማኔጅመንት ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 4 እንዲሁም በዲግሪ ሆቴል ማኔጅመንት፣ አካውንቲንግ እና ፋይናንስ፣ ማኔጅመንት፣ ማርኬቲንግ ማኔጅመንት እና በልዩ ልዩ የአጫጭር ጊዜ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን ከ1,100 በላይ ተማሪዎችን ዛሬ ነሃሴ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በግዮን ሆቴል አስመርቋል።
ከተመሰረተ በ10 አመታት ውስጥ ከ11ሺህ በላይ ተማሪዎችን አስመርቋል ያሉት የኮሌጁ ፕሬዝዳንት አቶ አንዱዓለም ተሾመ ከ1,200 በላይ ተማሪዎችን በነጻ በማስተማር ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣቱን ተናግሯል።
በተማሪዎች ምርቃት ስነ ስርዓት ላይ ለአርቲስት ሰለሞን ቦጋለ እና ለወይዘሮ ሙዳይ ምትኩ (የሙዳይ በጎ አድራጎት ማሕበር መስራች) የክብር ዲፕሎማ ሰጥቷል።
