መንግስት ለመጪው ምርጫ “ሰላማዊ የውድድር ሜዳ እንዲፈጥር” አራት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረቡ

Date:

በኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ አንድ ዓመት ከመቅረቱ አኳያ፤ ገዢው ፓርቲ “እውነተኛ” እና “ሁሉን አካታች” የሆነ ድርድር “በአስቸኳይ” በማድረግ እና በሀገር ውስጥ የተፈጠሩ ቀውሶችን በመፍታት፣ “ሰላማዊ የውድድር ሜዳ እንዲፈጥር” አራት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረቡ። ፓርቲዎቹ “ለሰላማዊ ትግል ውጤታማነት” እገዛ ለማድረግ፤ መንግስት “የፖለቲካ እስረኞችን” እንዲፈታም ጠይቀዋል።

ዛሬ ሰኞ ግንቦት 4፤ 2017 በጋራ ባወጡት መግለጫ ጥሪ፣ ጥያቄ እና ማሳሰቢያቸውን ያቀረቡት፤ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ)፣ የአማራ ግዮናዊ ንቅናቄ እና እናት ፓርቲ ናቸው። በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠው የአራቱ ፓርቲዎች የዛሬ መግለጫ ትኩረቱን ያደረገው፤ በ2018 ዓ.ም. ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ሰባተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ ነው። 

“ኢትዮጵያ ሀገራችን አሁን ካለችበት የጦርነት አዙሪት ለመውጣት እና የህዝብ ጭቆና፣ አፈና፣ ሰቆቃና እልቂትን ማስቆም የሚቻለው፤ ከማጭበርበር የጸዳ፣ ነጻ፣ ፍትሃዊና ተአማኒ ምርጫ በማካሄድ ብቻ መሆኑን እኛ በሰላማዊ መንገድ የምንታገል የትብብር ፓርቲዎች በጽኑ እናምናለን” ሲሉ ፓርቲዎቹ በመግለጫቸው ላይ አስፍረዋል። እነዚህን መስፈርቶች የሚያሟላ ምርጫ፤ በተፈጥሮው “ሰላማዊ የመከወኛ ሜዳ የሚሻ” መሆኑንም ጠቅሰዋል።

🔴 ለዝርዘሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15857/

@EthiopiaInsiderNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...

የእግር ኳስ ዳኝነት በኢትዮጵያ

ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ግዮን መጽሔት :- እግር ኳስ...

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...