ማክሮን ከሥልጣን የለቀቁትን ጠቅላይ ሚኒስትር መልሰው ሾሙ

Date:

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአራት ቀናት በፊት ሥልጣን የለቀቁትን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳግመኛ ሾሙ።

የፈረንሳዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰባስሽን ሌኮርኑ አንድ ወር ሳይሞላቸው ሥልጣን መልቀቃቸው ይታወሳል።

“ሥራውን አልፈልገውም፤ ኃላፊነቴን ጨርሻለሁ” ብለው ከሥልጣን የለቀቁት ሰባስሽን ሌኮርኑ ወደ ሥልጣን መመለሳቸው አነጋጋሪ ሆኗል።

በድጋሚ የተሾሙት ጠቅላይ ሚኒስትር እስከ ሰኞ ድረስ የቀጣዩን ዓመት በጀት ለፓርላማ ማቅረብ አለባቸው።

የ39 ዓመቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ከማክሮን ዋነኛ ደጋፊዎች አንዱ ናቸው።

በኤክስ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት “ፕሬዝዳንቱ በሰጡኝ ኃላፊነት መሠረት የፈረንሳይን በጀት ከማቅረብ ባሻገር ፈረንሳውያን ለሚገጥሟቸው ችግሮች መፍትሔ አበጃለሁ” ብለዋል።

ባለፈው ሳምንት “ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኜ ለመቀጠል የሚያስችል ሁኔታ አልተሟላም” ሲሉ ለሥልጣናቸው መልቀቅ ምክንያት የሆናቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...