ምርጫ ቦርድ የፓለቲከኞችን የምርጫ ክህሎት ለማሳደግ ሥልጠና መስጠት ጀመረ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኔዘርላንድ የመድብለ ፓርቲ የዲሞክራሲ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎች ለተውጣጡ ፓለቲከኞች በምርጫ ክርክር ክህሎት ላይ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

የሥልጠናው ዋንኛ ዓላማ ፓለቲከኞች ለመራጩ የሚያቀርቡት ማኒፌስቶ (ፓሊሲዎችና ፕሮግራሞች) የህዝብ ቅቡልነት እንዲያገኙ የፓለቲከኞች የምርጫ ክርክር ክህሎትን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነው።

በምርጫ ክርክር አማካኝነት ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች ለመራጩ ህዝብ በሚሰጡት አማራጭ የፓሊሲ አማራጮች ምክንያት መራጮች ዕውቀት ላይ ተመስርተው የሚበጃቸውን እንዲመርጡ ከማስቻሉ ባሻገር የዲሞክራሲ ተሳትፎ ባህልን ይጎለብታል።

በሥልጠና የመክፈቻ መርሃ ግብር ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ 7ኛውን ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ አንድ ዓመት ገደማ ነው የቀረን። ስለሆነም ይህ ስልጠና የክርክር ክህሎታችሁን በማጎልበት የተደራጀ የፓለቲካ ፕሮግራሞቻችሁን፣ ፓሊሲዎቻችሁን ለመራጩ በማስተዋወቅ እና በማሳመን፤ መራጩ መረጃና ዕውቀት ላይ ተመስርቶ እንዲመርጥ ያስችለዋል ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...