ታግተው የነበሩ 25 ኢትዮጵያዊያን ተለቀቁ

Date:

በየመን በኢትዮጵያዊያን ታግተው የነበሩ 25 ኢትዮጵያዊያን ተለቀቁ፡፡ ሳውዝ 24 የተሰኘው የየመን ሚዲያ እንደገለፀው እነዚህ ኢትዮጵያዊያን በሻብዋ ግዛት ውስጥ ታግተው የነበሩ ናቸው፡፡

የሻብዋ ግዛት ዋና ከተማ በሆነው አታቅ ምስራቃዊ ክፍል የአገራቸው ልጆች በሆኑ በኢትዮጵያዊያን ከታገቱ በኋላ ቤተሰቦቻቸው የማስቀቂያ ገንዘብ እንዲከፍሉ መጠየቃቸውንም አስረድቷል፡፡ ይህ መረጃ የደረሰው የሻብዋ ፖሊስ ባደረገው ክትትል ታጋቾቹ ያሉበትን ቦታ ከደረሰበት በኋላ በወሰደው እርምጃ 25ቱንም ኢትዮጵያዊያን ትላንት ምሽት ማስለቀቅ መቻሉንም አስታውቋል፡፡

እንደፖሊስ መግለጫ በአጋቾቹ ቤት ውስጥ ከታገቱት ከእነዚህ ኢትዮጵያዊያን በተጨማሪ 15 ሚሊዮን የየመን ሪያልና 55 ሺህ የሳኡዲ ሪያል ተገኝቷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...