በየመን በኢትዮጵያዊያን ታግተው የነበሩ 25 ኢትዮጵያዊያን ተለቀቁ፡፡ ሳውዝ 24 የተሰኘው የየመን ሚዲያ እንደገለፀው እነዚህ ኢትዮጵያዊያን በሻብዋ ግዛት ውስጥ ታግተው የነበሩ ናቸው፡፡
የሻብዋ ግዛት ዋና ከተማ በሆነው አታቅ ምስራቃዊ ክፍል የአገራቸው ልጆች በሆኑ በኢትዮጵያዊያን ከታገቱ በኋላ ቤተሰቦቻቸው የማስቀቂያ ገንዘብ እንዲከፍሉ መጠየቃቸውንም አስረድቷል፡፡ ይህ መረጃ የደረሰው የሻብዋ ፖሊስ ባደረገው ክትትል ታጋቾቹ ያሉበትን ቦታ ከደረሰበት በኋላ በወሰደው እርምጃ 25ቱንም ኢትዮጵያዊያን ትላንት ምሽት ማስለቀቅ መቻሉንም አስታውቋል፡፡
እንደፖሊስ መግለጫ በአጋቾቹ ቤት ውስጥ ከታገቱት ከእነዚህ ኢትዮጵያዊያን በተጨማሪ 15 ሚሊዮን የየመን ሪያልና 55 ሺህ የሳኡዲ ሪያል ተገኝቷል፡፡
