በህንድ እና ፓኪስታን ግጭት ሳቢያ የታቀደው የፓኪስታን ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ

Date:

በአዲስ አበባ በሚገኘው ሚሊኒየም አዳራሽ ከግንቦት 7 እስከ 9 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ሊካሄድ የነበረው “ሜድ ኢን ፓኪስታን” ኤግዚቢሽን ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም መደረጉ ተሰምቷል።

ይህ የንግድ ትርኢት ከ100 በላይ የሚሆኑ ታዋቂ የፓኪስታን አምራቾችን በማሳተፍ በጨርቃ ጨርቅ፣ በመድሃኒት፣ በኢንጂነሪንግ፣ እና በግብርና ምርቶች ማቀነባበርን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን የኤክስፖርት አቅም እና የፈጠራ ምርቶቻቸውን ለማሳየት ታቅዶ እንደነበር ይታወሳል።

ይሁን እንጂ የዝግጅቱ አዘጋጆች ባወጡት መግለጫ በቅርቡ በህንድ እና በፓኪስታን መካከል በተፈጠረው አስገዳጅ ሁኔታ ማለትም ግጭት ምክንያት ኤግዚቢሽኑ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም መደረጉን አሳውቀዋል።

ይህ የሶስት ቀናት ዝግጅት በፓኪስታን መንግስት በንግድ ሚኒስቴር፣ በፓኪስታን የንግድ ልማት ባለስልጣን (TDAP) እና በአዲስ አበባ በሚገኘው የፓኪስታን ኤምባሲ የንግድ ክፍል የተዘጋጀ ሲሆን የንግድ-ለ-ንግድ (B2B) ግንኙነቶችን ለማጠናከር እና ጠቃሚ ሽርክናዎችን ለመፍጠር ምቹ መድረክ ለመፍጠር ታቅዶ ነበር።

አዘጋጆቹ ይህንን በቀጣይ ስለ ዝግጅቱ የሚኖር ሂደት በደብዳቤ ለሚመለከታቸው አካላት የሚገለጽ መሆኑንም አሳውቀዋል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...