በመዲናዋ 163 ቢሊየን ብር ገቢ ተሰበሰበ

Date:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት 163 ቢሊየን ብር ገቢ ሰበሰበ፡፡

የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት÷ በበጀት ዓመቱ የከተማዋን የገቢ አማራጮች በአግባቡ በመጠቀም ረገድ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል፡፡

በዚህም በዓመቱ መጨረሻ 156 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 163 ቢሊየን ብር መሰብሰበ መቻሉን ነው የተናገሩት፡፡

ገቢው ከቀጥታ ታክስ፣ ቀጥተኛ ካልሆነ ታክስ፣ ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት እና ከሌሎች መሰብሰቡን አስረድተዋል።

በቀጣይ የከተማዋ ኢኮኖሚ ማመንጨት በሚችለው ልክ ገቢ ለመሰብሰብ የተለያዩ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ለመተግበር ዝግጅት ተደርጓል ነው ያሉት፡፡

በተለይም በግብር አሰባሰብ ሒደት ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችን መፍታት የሚያስችሉ 24 አዳዲስ አሰራሮችን ወደ ሥራ ለማስገባት በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...