በማይናማር አስቸጋሪ ሁኔታ ዉስጥ የነበሩ 1 ሺህ 300 የሚሆኑ ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት ተመልሰዋል

Date:

በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ዉስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ወደ ሀገር ለመመለስ እየተሰራ ቢገኝም አስቸጋሪ ሁኔታ እንዳለ እያወቁ የስራ እድል አለ በሚል የሚሄዱ ዜጎች እያጋጠሙት መሆኑን ዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።

ሆኖም በህጋዊ መንገድም ሄደዉ ችግር የሚያጋጥማቸው ኢትዮጵያውያንን መብት ለማስጠበቅ ቆንስላ እና ኤምባሲ ትኩረት ሰጥተዉ እንዲከታተሉ ቋሚ የስራ መመሪያ ተሰጥቷል ተብሏል።

የኢትዮጵያዉያኑ ክብር እና መብት ተጠብቆ እንዲቆዩ ከሚሲዮን መሪዎች በተጨማሪ ይህንን ጉዳይ ብቻ እንዲከታተሉ ዲኘሎማቶች መመደባቸዉን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ተናግረዋል።

ከማይናማር በተጨማሪ በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታዉ ነበሩ የተባሉ 26 ሺህ ዜጎችን በአምስት ወራት ዉስጥ ማስመለሱን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ለስራ የተጓዙ ኢትዮጵያዉያን ከአንድ የስራ ቦታ ወደ ሌላ የስራ ቦታ ለመለወጥ ወይም ወደ ሀገር ለመመለስ እንዲሁም የካሳ ክፍያ እንዲያገኙ እንዲሁም ከደሞዝ ጋር የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ነዉ ተብሏል።

በጅዳ፣ ሪያድ ፣አቡዳቢ፣ዱባይ እንዲሁም በኩዌት ቆንስላ ፅ/ቤት ይህንን ለማድረግ እየተሰራ ነዉ ብለዋል።

ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ያልሄዱ እና ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ የስራ ስምምነት ያላደረገችበት የስራ ጉዞ ያደረጉ ዜጎች ለዘርፈ ብዙ ጥቃት የተዳረጉ መሆናቸዉ ተገልጿል።

የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ዛሬ በእንደራሴዎች ምክር ቤት ተገኝተው ከአባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...