በሞሮኮ ራባት በተካሄደው የሴቶች 1 ሺህ 500 ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ አሸንፋለች፡፡
አትሌት ፍሬወይኒ ርቀቱን 3 ደቂቃ 58 ሰከንድ ከ25 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ነው ቀዳሚ የሆነችው፡፡
በርቀቱ የተሳተፈችው ሌላኛዋ አትሌት ሐረገወይን ካልአዩ ደግሞ 3 ደቂቃ 59 ሰከንድ ከ28 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች፡፡
በሌላ በኩል በሴቶች 800 ሜትር ውድድር አትሌት ፅጌ ድጉማ በ1 ደቂቃ 57 ሰከንድ ከ24 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 2ኛ ሆናለች፡፡
