ኢራን በአካባቢው ላይ ከሚደረጉ ማናቸውንም ግድየለሽነት የተሞሉ እንቅስቃሴዎች አስጠነቀቀች

Date:

በፋርስ ባሕረ ሰላጤ፣ በኦማን ባሕር ወይም በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ሁኔታዎችን ይበልጥ የሚያወሳስብ ማንኛውም ዓይነት ዕርምጃ ጥበብ የጎደለው መሆኑንና ማንኛውም ኃላፊነት የሚሰማው ወይም ምክንያታዊ የሆነ አካል እንዲህ ዓይነቱን አደገኛ ዕርምጃ አይወስድም ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

ዋና ዋና መግለጫዎች፦

🟠 የኔቶ እና የአውሮፓ ኅብረት አገራት እውነትም ኃላፊነታቸውን መወጣት የሚፈልጉ ከሆነ፤ ለቀውሱ ዋነኛ መንስኤ የሆኑትን አሜሪካንና እስራኤልን ተጠያቂ ማድረግ አለባቸው።

🟠 የአሜሪካ እና የእስራኤል ወታደራዊ ትንኮሳ ከመከሰቱ በፊት፣ በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል መደበኛ የባሕር ላይ ትራፊክ በሰላም ይንቀሳቀስ ነበር።

🟠 ኢራን፣ የባሕር ዳርቻ አገር እንደመሆኗ መጠን፣ ደኅንነቷንና ብሔራዊ ጥቅሟን ለመጠበቅ አስፈላጊ የሆኑ ዕርምጃዎችን ለመውሰድ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ሙሉ መብት አላት።

🟠 መርከቦች አስተማማኝ ጉዞን ለማረጋገጥ ከኢራን ጦር ኃይል ጋር ቅንጅት በመፍጠር በሰርጡ በኩል መጓዛቸውን ቀጥለዋል።

🟠 ዋሽንግተን በቅርቡ በዓለም አቀፍ የንግድ መርከቦች ላይ ያደረገችው ሕገ-ወጥ ጣልቃገብነት ሁኔታውን ይበልጥ አባብሶታል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...