በቀዶ ጥገና 3.5 ኪሎ ግራም ክብደት ያለው ስብም ወጣ

Date:

የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል በሰውነቱ ላይ አላስፈላጊ የስብ ክምችትን ወይም በህክምና ስያሜው ‘Madelung’s Disease’ የነበረበትን የ40 ዓመት ግለሰብ የቀዶ ጥገና ህክምና በተሳካ ሁኔታ ማከናወኑን ገልጿል።

የቀዶ ጥገና ህክምናውን ዶ/ር ኦብሳ ቢራቱ ሲመሩት ለማጠናቀቅ 5 ሰዓታትን ፈጅቷል።

ግለሰቡ በአንገቱ አካባቢ የተከማቸው ስብ ወደ ደረቱ ወርዶ የመተንፈሻ ችግር እንዲገጥመው አድርጎት ነበር።

ከቀዶ ጥገናው በኋላ 3.5 ኪሎ ግራም ክብደት ያለው ስብም ከሰውነቱ ወጥቷል።

ታካሚው ከቀዶ ጥገናው በኋላ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል።

የቀዶ ጥገናውን ያከናወኑ ሃኪሞች ቡድን

  1. ዶ/ር ኦብሳ ቢራቱ
  2. ዶ/ር ሲንቦና አራርሳ
  3. ዶ/ር ብርሃኑ ንጉሴ
    እንደዚሁም በአንኤስቴሺያ ዶ/ር ኡስማን እና ዶ/ር መኩሪያ ተሳትፈዋል።

በነርስነት አብዲ፣ ዲቤ፣ ዋቅጅራ እና ተሬሳ የተባሉ የጤና ባለሙያዎች ስለመሳተፋቸው የአምቦ ዩኒቨርስቲ ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...