ቢሮዉ በመካከለኛ ምስራቅ በተከሰተዉ ቀዉስ ምክንያት የተፈጠረዉን የነዳጅ እጥረት ለመከላከል በነዳጅ ማዲያዎች ቅድሚያ አገልግሎት የሚያገኙ ተቋማትን ይፋ አደርጓል፡፡
በዚህም መሰረት
👉ለነዳጅ አጓጓዥ ተሽከርካሪዎች/ ቦቴዎች፤
👉ለከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች፤መሰረታዊ የምግብ ፍጆታ ምርቶች እና የኤክስፖርት ምርቶችን የሚያመርቱ፤
👉ግንባታ ላይ ላሉና ትኩረት ለሚሰጣቸዉ የመንግስትና የግል ፕሮጀክቶች፤
👉ለደረቅ ጭነት እና ለግንባታ ቁሳቁስ አጓጓዥ ተሽከርካሪዎች (ገበያ ለማረጋጋት የግብርናና ኢንዱስትሪ ፍጆታ ምርቶች የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎችን ይጨምራል)
👉ለግብርና ማሽነሪዎች / ትራክተሮች
👉ለሀገር አቋራጭ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች
👉ለከተማ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች
👉ለሕብረተሰብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ( አምቡላንስ፡ ቀዶ ጥገና የሚሰሩ ተቋማት፡ መብራት)
👉ሌሎች እንደአስፈላጊነቱ በንግድ ቢሮ እየቀረበ በግብረ ሃይል እየታየ ዉሳኔ ሲሰጥ የሚጨመር መሆኑን ቢሮዉ ገልጿል።
