በአሜሪካ ቪዛ ያላቸው የውጪ ሃገር ዜጎችን ቪዛ መመርመር ተጀመረ

Date:

የትራምፕ አስተዳደር እነዚህ የአሜሪካ ቪዛ ያላቸው 55 ሚሊየን የውጪ ሃገር ዜጎች ከሃገር ሊያስባርራቸው የሚችል ጥፋት መስራታቸውን እየመረመረ ነው ተብሏል።

የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሁሉም የአሜሪካ ቪዛ ያላቸው ሰዎች ተከታታይነት ያለው ምርመራ እንደሚደረግባቸውና ጥፋት ከተገኘባቸው ቪዛቸው እንደሚሰረዝ እና ከአሜሪካ እንደሚባረሩ ገልጿል።

የትራምፕ አስተዳደር ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ህገወጥ ያላቸውን ስደተኞች ከአሜሪካ እያባረረ የቆየ ሲሆን በተለያዩ ሃገራት ዜጎች ላይም የቪዛ እገዳዎችን ሲጥል ቆይቷል።

የአሁኑ ውሳኔ ደግሞ ሁሉም የአሜሪካ ቪዛ ያለው የውጪ ዜጋ ላይ ምርመራ መጀመሩን ሲያሳይ በርከት ያሉ የአሜሪካ ቪዛ የያዙ ሰዎችንም ስጋት ውስጥ ከቷል።

የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ለአሸባሪ ድርጅቶች ድጋፍ ማድረግን ጨምሮ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ የቆዩና በወንጀል ተግባር የተሳተፉ ሰዎች እንደዚሁም ማህበራዊ ሚዲያን ጨምሮ በየትኛውም መንገድ የፀረ አሜሪካ እይታን ያንፀባረቁ ሰዎች በየተኛውም ጊዜ ቪዛቸው ሊሻር እንደሚችልና ከአሜሪካ ሊባረሩ እንደሚችሉ አስጠንቅቋል።

ባለፈው አመት በአሜሪካ 12.8 ሚሊየን ሰዎች የግሪን ካርድ የነበራቸው ሲሆን 3.6 ሚሊየን ሰዎች ደግሞ በጊዜያዊ ቪዛ በአሜሪካ ቆይተዋል።

Source: AP, The Guardian

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...