በኢትዮጵያ የ1 ግራም ወርቅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በማሻቀብ ወደ 29,900 ብር መድረሱ ተነገረ። ካፒቲል ያደረገዉ የገበያ ቅኝት እንደሚያመለክተው፣ የአንድ ግራም ወርቅ ዋጋ በደረሰኝ (ከታክስ ጋር) ሲሰላ እስከ 29,900 ብር ደርሷል። የወርቁ ዋጋ ብቻዉን (ታክስ ሳይጨመር) ደግሞ 26,000 ብር ሆኗል።
በተመሳሳይ፣ አንዳንድ የሀገር ውስጥ ገበያ ዋጋዎች እንደሚጠቁሙት የወርቁ ዋጋ 25,000 ብር ሆኖ፣ ከእነ ደረሰኝ ሲሰላ ደግሞ 28,750 ብር መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።
ይህ የወርቅ ዋጋ መጨመር በሀገር ውስጥ ያለውን የዋጋ ግሽበት እና ዓለም አቀፍ የወርቅ ገበያ መለዋወጥን የሚያመለክት እንደሚሆን ባለሞያዎች አስረድተዋል።
በተለይ የዋጋዉ መለዋወጥ የተስተዋለዉ ከሳምንታት በፊት ሲሆን ይህም በአንዱ የወርቅ ዋጋ ላይ ከ 2 ሺህ እስከ 3 ሺህ ብር ጭማሪ መደረጉን ካፒታል ሰምቷል።
የዚህ የዋጋው መናር በጌጣጌጥ ገበያ እና በወርቅ ተጠቃሚዎች ላይ ተጽዕኖ እንደሚፈጥር የሚናገሩት ባለሞያዎቹ አሁን የዚህ የዋጋ መለዋወጥ የሚቀጥል እንደሚሆን አፅንኦት በመስጠት ተናግረዋል።
