በወንጀል ድርጊት ስለሚገኘ ንብረትን ጉባዔ እየተካሄደ ነው

Date:


የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ/ ንብረትን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል መከላከል ቡድን 50ኛ የከፍተኛ ሃላፊዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡


በጉባዔው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሐይ ጳውሎስ፣ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሙሉቀን አማረ እና የቡድኑ ሊቀ መንበር ፍሬዘር አያሌው ተገኝተዋል፡፡


የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል መከላከል ቡድን ዓመታዊ ጉባዔ ከነሐሴ 16 እስከ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።


በዛሬው ዕለት የተጀመረው የቡድኑ ከፍተኛ ሃላፊዎች ጉባዔም የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል መከላከል ቡድን ዓመታዊ ጉባዔ አካል ነው፡፡


በጉባዔው ከአባል ሀገራቱ፣ ከአንድ ታዛቢ ሀገር እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት የተወጣጡ 1 ሺህ 150 በላይ ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡


ኢትዮጵያ በቀጣናው በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል መከላከል ላይ በንቃት እየተሳተፈች እንደምትገኝ በመድረኩ ተነስቷል፡፡


በዘርፉ የሕግ ማሻሻያ ከማድረግ ጀምሮ ከተለያዩ ሀገራት ጋር በትብብርና በቅንጅት እየሰራች መሆኑም ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...