የኢትዮ ቴሌኮምና የዜድ ቲ ኢ ግዙፍ የኔትወርክ ማስፋፊያ ስምምነት

Date:

በስፔን ባርሴሎና እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የሞባይል ዓለም አቀፍ ኮንግረስ ጎን ለጎን፣ ኢትዮ ቴሌኮም የኔትወርክ አቅሙን ለማዘመንና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት የሚያስችል ግዙፍ ስምምነት ከቻይናው ዜድ ቲ ኢ (ZTE) ኮርፖሬሽን ጋር ተፈራርሟል፡፡

በዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ፍሬሕይወት ታምሩ የተፈረመው ይህ ፕሮጀክት በአጠቃላይ 647 አዳዲስ የኔትወርክ ጣቢያዎችን መገንባትን የሚያካትት ሲሆን፣ በዋናነትም ዘመናዊ የሞባይል ብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው የገጠር አካባቢዎች ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የሀገሪቱን የ4ጂ የሕዝብ ሽፋን ወደ 95.5 በመቶ በማሳደግ የአገልግሎት ጥራትን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሻሽል ይጠበቃል፡፡

ስምምነቱ የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ከማፋጠኑ ባለፈ፣ የዲጂታል ሥነ-ምህዳሩን በማዘመን ረገድ የላቀ ሚና ይጫወታል።

ይህ ስምምነት ኩባንያው ከኤሪክሰን ጋር ካደረገው ተመሳሳይ የቴክኖሎጂ አጋርነት ጋር ተዳምሮ የኢትዮጵያን የቴሌኮም መሠረተ ልማት ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ታምኖበታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...