ለ22 ዓመታት ለኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ትልቅ አስተዋፅዖ እንዳበረከተ የሚነገርለት ዓለም ሲኒማ፤ አሁን ደግሞ ለመገናኛና አካባቢው የፊልም ተመልካች በማራቶን የገበያ ማዕከል ሁለተኛ ፎቅ ላይ ደረጃውን የጠበቁ ሁለት ሲኒማ ቤቶችን ከፍቷል፡፡
ቅዳሜ በተደረገው የምርቃት ስነስርዓት ላይ የአዲስ አበባ ባህልና ኪነጥበብ ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ሂሩት ካሣ እንዲሁም የኪነጥበብ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ዓለም ሲኒማ በመገናኛ ሁለት ደረጃቸውን የጠበቁ ሲኒማ ቤቶችን በ120 ሚሊየን ብር ወጪ የገነባ ሲሆን፤ በአጠቃላይ ከ550 በላይ ተመልካቾችን የማስተናገድ አቅም እንደለው ተነግሯል፡፡
ሲኒማ ቤቶቹ ከፍተኛ የምስል ጥራት ያላቸው፣ ዘመናዊ ሳውንድ ሲስተም የተገጠመላቸው እንዲሁም ምቹና ውብ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
በሁለቱም ሲኒማ ቤቶች ከሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የተለያዩ ሀገርኛ ፊልሞች ለዕይታ ይቀርባሉ ተብሏል፡፡
