ባርኮድ የተካተተበት ደረሰኝ ለማሳተም በ6 ቀናት ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ተገለፀ

Date:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ባርኮድ የተካተተበት ደረሰኝ ለማሳተም እስካሁን በተለያዩ ምክንያቶች ያላቀረቡ ግብር ከፋዮች ጥያቄ የማቅረቢያ ጊዜ ሊጠናቀቅ የቀሩት 6 ቀናት ብቻ መሆኑን ገልጿል፡፡

ቢሮው በአዲስ አበባ ከተማ ባርኮድ የተካተተበት ደረሰኝ ለማሳተም ጥያቄያቸውን በማቅረብ አሳትመው መጠቀም የሚጠበቅባቸው 113 ሺህ 37 የደረጃ “ሀ” ፣ የደረጃ “ለ” እና በፈቃደኛነት ደረሰኝ የሚጠቀሙ የደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች አሉ ሲልም ገልጿል።

ይሁን እንጂ እስከ አሁን ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑ ግብር ከፋዮች ጥያቄያቸውን ያላቀረቡ መሆናቸውን አመላክቷል።

ስለሆነም ልዩ መለያ ኮድ የተካተተበትን ደረሰኝ ለማሳተም ሁሉም ግብር ከፋይ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ብቻ ጥያቄውን ማቅረብ እንደሚጠበቅበት ማስታወቁን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የፌዴራል ገቢዎች ሚኒስቴር የክልሎችን እና የሁለቱን የከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ጥያቄዎችን መነሻ በማድረግ ባርኮድ የተካተተበት ደረሰኝ ለማሳተም ግብር ከፋዩ ጥያቄውን የማቅረቢያ ጊዜን በአንድ ወር በማራዘም የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲጠናቀቅ መወሰኑ የሚታወስ ነው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...