ትራምፕ፤ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ እንዲኖራት “አልፈቅድም” አሉ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ እንዲኖራት እንደማይፈቅዱ በመግለጽ አገሪቱ የኒውክሌር መርሃ ግብሯን ለመግታት እንድትስማማ አስጠነቀቁ።

ትራምፕ ለኮንግረስ አባላት ባደረጉት ንግግር “የእኔ ምርጫ ችግሩን በዲፕሎማሲ መፍታት ነው። አንድ ጉዳይ ግን እርግጥ ነው። እሱም፤ የዓለም ቁጥር አንድ የሽብር ደጋፊ የኒውክሌር መሣሪያ እንዲኖራት አልፈቅድም” ብለዋል።

ሁለት ሰዓት ገደማ በቆየው የ ‘ስቴት ኦፍ ዘ ዩኒየን’ ንግግራቸው ላይ እንደገለጹት፤ ኢራን በአሜሪካ ተጨማሪ ጥቃት እንዳይሰነዘርባት በሚል ስምምነት ላይ መድረስ ትፈልጋለች።

ሆኖም ግን ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ ግንባታን በተመለከተ ምንም ስምምነት እንዳላደረገች አክለዋል።

አሜሪካ በመካከለኛው ምሥራቅ ግዙፍ የጦር መርከቦቿን ማሰማራቷን ተከትሎ ከኢራን ጋር ግጭት ይፈጠራል የሚል ስጋት አንዣቧል።

ትራምፕ በዛሬው ንግግራቸው ኢራን ታጣቂዎችን እንደምትደግፍ እንዲሁም ተቃዋሚዎችን እንደገደለች ገልጸዋል።

በተጨማሪም “የኢራን መንግሥት እና ገዳይ የሆኑት አጋሮቹ ሽብር፣ ሞት እና ጥላቻን ነዝተዋል” ማለታቸውን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።

ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው ኢራን ላይ ሊወሰድ ስለሚችል እርምጃ ቢገልጹም ዝርዝር መረጃዎችን አልሰጡም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...