ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፈን ሀሰን በላውራ አዋርድ እጩ ሆና ቀረበች

Date:


በየአመቱ ስኬታማ ጊዜን ያሳለፉ ስፖርተኞች እውቅና የሚያገኙበት የላውራ አዋርድ በፓሪስ ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ያገኙ 6 አትሌቶች እጩ ሆነው ቀርበውበታል።

በሴቶች ለኔዘርላንድስ የምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሲፈን ሀሰን ዕጩ ስትሆን አትሌቷ በፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን የወርቅ በ5ሺ እና በ10ሺ ደግሞ የነሀስ ሜዳልያ ማሳካቷም ይታወሳል።

በፓሪስ 2024 በ1500 ሜትር የወርቅና በ5ሺ ሜትር የብር ሜዳልያ ያገኝችው ኬንያዊቷ ፌዝ ኪፕየጎን አሜሪካዊቷ ማክ ላህሊን ሌቭሮን እና የሴንት ሉቺያዋ ጁሊያን አልፍሬዝ በሴቶች ዘርፍ በእጩነት የቀረቡ ሆነዋል።

በወንዶች ዘርፍ ደግሞ የምርኩዝ ዘላዩ ሙንዶ ዱፕላቲን እና የአጭር ርቀት ሯጩ የቦትስዋናው ሌትሲል ቴቦጎ ታጭተዋል።

በ7 ዘርፎች እውቅና በሚሰጥበት የላውራ ሽልማት ከአትሌቲክሱ ውጭ ሲሞን ባይልስ እና ካርሎስ አልካሬዝን ጨምሮ በርካቶች በእጩነት ተካተዋል።

ለ25ኛ ጊዜ በሚካሄደው ላውራ አዋርድ የመጨረሻው አሸናፊ ሚያዚያ 13 ቀን በማድሪድ የሚታወቅ ይሆናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...