ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፈን ሀሰን በላውራ አዋርድ እጩ ሆና ቀረበች

Date:


በየአመቱ ስኬታማ ጊዜን ያሳለፉ ስፖርተኞች እውቅና የሚያገኙበት የላውራ አዋርድ በፓሪስ ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ያገኙ 6 አትሌቶች እጩ ሆነው ቀርበውበታል።

በሴቶች ለኔዘርላንድስ የምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሲፈን ሀሰን ዕጩ ስትሆን አትሌቷ በፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን የወርቅ በ5ሺ እና በ10ሺ ደግሞ የነሀስ ሜዳልያ ማሳካቷም ይታወሳል።

በፓሪስ 2024 በ1500 ሜትር የወርቅና በ5ሺ ሜትር የብር ሜዳልያ ያገኝችው ኬንያዊቷ ፌዝ ኪፕየጎን አሜሪካዊቷ ማክ ላህሊን ሌቭሮን እና የሴንት ሉቺያዋ ጁሊያን አልፍሬዝ በሴቶች ዘርፍ በእጩነት የቀረቡ ሆነዋል።

በወንዶች ዘርፍ ደግሞ የምርኩዝ ዘላዩ ሙንዶ ዱፕላቲን እና የአጭር ርቀት ሯጩ የቦትስዋናው ሌትሲል ቴቦጎ ታጭተዋል።

በ7 ዘርፎች እውቅና በሚሰጥበት የላውራ ሽልማት ከአትሌቲክሱ ውጭ ሲሞን ባይልስ እና ካርሎስ አልካሬዝን ጨምሮ በርካቶች በእጩነት ተካተዋል።

ለ25ኛ ጊዜ በሚካሄደው ላውራ አዋርድ የመጨረሻው አሸናፊ ሚያዚያ 13 ቀን በማድሪድ የሚታወቅ ይሆናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...