አሜሪካ የኢራን ወደቦችን ለመዝጋት ማቀዷን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ

Date:



አሜሪካ ወደ ኢራን ወደቦች የሚገቡና የሚወጡ መርከቦችን ለማገድ የባሕር ላይ ከበባ እንደምታደርግ ማስታወቋን ተከትሎ፤ ሰኞ ሚያዝያ 05 ቀን 2018 ዓ.ም. በማለዳው የገበያ ግብይት የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።

አልጀዚራ እንደዘገበው፤ የአሜሪካ ድፍድፍ ነዳጅ (US crude oil) ዋጋ 8 በመቶ በመጨመር በአንድ በርሜል 104.24 ዶላር ደርሷል።

የዓለም አቀፍ መለኪያ የሆነው የብሬንት (Brent) ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋም በ7 በመቶ ጭማሪ በማሳየት በበርሜል 102.29 ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል።

ዓለማቀፉ ግዙፍ የኢነርጂ ገበያ ተንታኝ ኦኒክስን (Onyx) ዋቢ በማድረግ ብሉምበርግ እንደዘገበው ደግሞ፤ አሜሪካ የባሕር ላይ ከበባውን የምትቀጥል ከሆነ ዓለማቀፍ የነዳጅ ዋጋ እስከ 150 ዶላር ሊያሻቅብ ይችላል።

የአሜሪካና የእስራኤል ጥቃት በኢራን ላይ በየካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ከመጀመሩ በፊት፤ በአንድ በርሜል 70 ዶላር ገደማ ይሸጥ የነበረው የብሬንት ነዳጅ ዋጋ፤ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ፤ ከፍተኛ መዋዠቅ የታየበት ሲሆን፤ በአንድ በርሜል እስከ 119 ዶላር ደርሶ እንደነበር ይታወሳል።

ባለፈው ሳምንት ዓርብ ሚያዝያ 03 ቀን 2018 ዓ.ም. አሜሪካ እና ኢራን በፓኪስታን ንግግር ከማድረጋቸው በፊት፤ ለሰኔ ወር የሚቀርብ የብሬንት ነዳጅ ዋጋ በ0.8 በመቶ ቀንሶ በበርሜል 95.20 ዶላር ነበር።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...