‘ኢራን በአሜሪካ ዲፕሎማሲ ላይ እምነት የላትም’

Date:

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለኢራን ባለሥልጣናት የድርድር ዕቅዳቸውን መላካቸውን እየገለጹ ባለበት ጊዜ ኢራን በአሜሪካ ላይ እምነት እንደሌላት ገለጸች።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ለሕንዱ ጋዜጣ ‘ኢንዲያ ቱዴይ’ በሰጡት ቃለ ምልልስ “ማንም በአሜሪካ ዲፕሎማሲ ላይ ዕምነት ሊጥል አይችልም” በማለት ያላቸውን ጥርጣሬ ገልጸዋል።

ጨምረውም “የአሜሪካንን ዲፕሎማሲ በተመለከተ ኢራን በጣም መጥፎ ልምድ አላት” በማለት በዘጠኝ ወራት ውስጥ ድርድሮች እየተካሄዱ ሁለት ጊዜ ጥቃት እንደተፈጸመባት በማብራራት ድርጊቱን “የዲፕሎማሲ ክህደት” ብለውታል።

ቃል አቀባዩ እንዲሁም “በአሜሪካ እና በኢራን መካከል እየተካሄደ ያለ ድርድር እንደሌለ” አጽንኦት በመስጠት አስተባብለው፤ በአሁኑ ጊዜ የኢራን ጦር ኃይሎች ትኩረታቸውን ያደረጉት “የአገሪቱን ግዛት በመከላከል” ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

አንድ ወር ሊሞላው የተቃረበውን አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የሚያካሂዱት ጦርነትን ለማብቃት ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአምስት ቀናት የጊዜ ገደብ አስቀምጠው የድርድር ነጥቦችን ማቅረባቸውን ገልጸዋል።

አስካሁን ግን ከኢራን በኩል ስለድርድሩ በይፋ የተባለ ነገር ካለመኖሩ በተጨማሪ የተለያዩ የአገሪቱ ባለሥልጣናት የተጀመረ ንግግር እንደሌለ እየተናገሩ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...