ኢራን በፈጸመቻቸው የሚሳኤል ጥቃቶች 89 እስራኤላውያን መጎዳታቸው ተነገረ

Date:

ኢራን በዛሬው ዕለት በፈጸመቻቸው የሚሳኤል ጥቃቶች የተጎዱ ሰዎች ቁጥር ወደ 89 ከፍ ማለቱን የእስራኤል የድንገተኛ አደጋ አገልግሎት ማጌን ዴቪድ አዶም አስታወቀ።

በተጨማሪ በቴልአቪቭ እና በደቡብ የሃገሪቱ ክፍል የተወነጨፉ ሮኬቶች ሶስት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሳቸውን እንዲሁም ሁለቱ ደግሞ በመካከለኛ ሁኔታ ላይ ናቸው ብሏል።

አብዛኛዎቹ የተጎዱት በፍንዳታዎች እንዲሁም በስብርባሪ እና ፍንጣሪዎች መሆኑን የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ።

በእስራኤል ደቡባዊ ክፍል ቤርሼባ በተሰኘች ከተማ የሚገኝ ሆስፒታል በኢራን የሚሳኤል ጥቃት ተመትቷል።

ኢራን የሚሳኤል ጥቃቱ ኢላማ በሆስፒታሉ አቅራቢያ የሚገኝ ወታደራዊ ይዞታ መሆኑን አስታውቃለች።
BBC  Amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...