ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ልታካሂድ ነው

Date:

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ መላ አገሪቱን የሚያዳርስ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለማካሄድ ዝግጅት እያደረገች ነው። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018 ዓ.ም. ለሚካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጀመሩን ይፋ አድርጓል።

ይህ ቆጠራ ከመስከረም ወር ጀምሮ በመላው አገሪቱ ከትናንሽ እስከ ትላልቅ የምርትና የንግድ ድርጅቶች ላይ የሚካሄድ በመሆኑ፣ በየደረጃው ያለው የመንግሥት አደረጃጀት፣ የኢኮኖሚ ድርጅት ባለቤቶች እንዲዘጋጁ ተጠይቋል።

የቅድመ ዝግጅት ተግባራት የቆጠራውን ስነ ዘዴ ማዘጋጀት፣ የሰው ኃይል ማሰልጠን፣ ለመስክ ሥራ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ማሟላትና የቴክኖሎጂ ዝግጅትን ማካተት እንደሚያጠቃልል ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...