ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ መላ አገሪቱን የሚያዳርስ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለማካሄድ ዝግጅት እያደረገች ነው። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018 ዓ.ም. ለሚካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጀመሩን ይፋ አድርጓል።
ይህ ቆጠራ ከመስከረም ወር ጀምሮ በመላው አገሪቱ ከትናንሽ እስከ ትላልቅ የምርትና የንግድ ድርጅቶች ላይ የሚካሄድ በመሆኑ፣ በየደረጃው ያለው የመንግሥት አደረጃጀት፣ የኢኮኖሚ ድርጅት ባለቤቶች እንዲዘጋጁ ተጠይቋል።
የቅድመ ዝግጅት ተግባራት የቆጠራውን ስነ ዘዴ ማዘጋጀት፣ የሰው ኃይል ማሰልጠን፣ ለመስክ ሥራ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ማሟላትና የቴክኖሎጂ ዝግጅትን ማካተት እንደሚያጠቃልል ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
CapitalNews
