ኢትዮጵያ እና ብሩንዲ በምዕራባውያን የቀረበውን የዩክሬን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ አደረጉ

Date:

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት 61ኛው መደበኛ ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ እና ብሩንዲ በምዕራባውያን አገራት አነሳሽነት የቀረበውን የዩክሬን የውሳኔ ሃሳብ በመቃወም ድምፅ ሰጥተዋል።

በጄኔ በተካሄደው በዚህ ስብሰባ ላይ የቀረበው ሰነድ በዩክሬን ያለውን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ የሚከታተለው ዓለም አቀፍ መርማሪ ኮሚሽን የሥራ ዘመን ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲራዘም የሚጠይቅ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ ኩባ ፣ ቻይና እና ብሩንዲ የውሳኔ ሃሳቡን ውድቅ አድርገውታል።

ምንም እንኳን የውሳኔ ሃሳቡ በዋናነት በኔቶ እና በአውሮፓ ህብረት አባል አገራት ድጋፍ ቢጸድቅም፣ እንደ ኬንያ፣ ግብፅ፣ አንጎላ እና ደቡብ አፍሪካ ያሉ 18 አገራት ድምፅ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

የውሳኔ ሃሳቡ ይዘት ሩሲያ ወታደሮቿን ከዩክሬን እንድታስወጣ የሚጠይቅና የዩክሬንን የግዛት አንድነት የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ ሩሲያ በበኩሏ የምርመራ ኮሚሽኑን “አድሏዊ እና ፖለቲካዊ ዓላማ ያለው ነው” በማለት ስትቃወም ቆይታለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...