ሀገራችን ኢትዮጵያ ራሷን ከ 17ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ሴካፋ ዞን ማጣሪያ ውድድር ማግለሏ ይፋ ተደርጓል።
ኢትዮጵያ ከውድድሩ ራሷን ያገለለችው በበጀት እጥረት መሆኑን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ለሴካፋ በላከው ደብዳቤ ገልጿል።
የኢትዮጵያ ከ 17ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በምድብ አንድ ከዩጋንዳ ፣ ታንዛኒያ እና ቡሩንዲ ጋር ተደልድሎ ነበር።
ይህንንም ተከትሎ የማጣሪያ ውድድሩ ምድብ አንድ በሶስት ሀገራት መካከል የሚካሄድ ይሆናል።
