ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጠናን ትግበራ ለመምራት ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ማቋቋሟ ተሰማ

Date:

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጠናን ስምምነት ወደ ሙሉ ትግበራ ለማስገባት የሚያስችል ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ማቋቋሟን አስታዉቃለች።

ይህ ኮሚቴ ከ55 የአፍሪካ አገራት ጋር የ1.4 ቢሊዮን ሕዝብ እና የ3.4 ትሪሊዮን የአሜሪካን ዶላር ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) ያለውን ግዙፍ የአህጉር ገበያ ለመጠቀም የሚያስችለውን እንቅስቃሴ በቅንጅት ይመራል ተብሏል።

በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሚመራው ይህ ኮሚቴ የገንዘብ ሚኒስቴርን፣ የብሔራዊ ባንክን፣ የጉምሩክ ኮሚሽንን፣ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴርን እንዲሁም የግሉን ዘርፍ ተወካዮችን ጨምሮ ቁልፍ ተቋማትን ያካተተ ሲሆን፣ የትግበራ ሂደቱን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ንኡሳን ኮሚቴዎችንም አቋቁሟል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንደገለፀዉ ፤ አገሪቱ ለትግበራ ዝግጅቷ ማጠናቀቂያ ከደረሱት ስራዎች መካከል 97% የሚሆኑት የታሪፍ መስመሮች በሂደት ወደ ዜሮ ታሪፍ እንዲወርዱ ተወስኗል ብሏል። በተጨማሪም የጉምሩክ ኮሚሽን ለኤክስፖርት የሚላኩ ምርቶች የምስክር ወረቀት የመስጠት ስራውን ማጠናቀቁን ለመረዳት ተችሏል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...