የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረ መስቀል፣ የአውሮፓ ኅብረት ሀገራቸውን “ለመቅጣት” የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤትን “እንደ መሣሪያ” እንደሚጠቀም ከሰሱ።
ሚኒስትሩ ዋና መቀመጫውን በጄኔቭ ያደረገውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት፣ “እየከሰመ ያለ ዓለም አቀፍ ሥርዓት ቅሪት” ሲሉ አጣጥለውታል፡፡
“ለራሳቸው የሞራል ልዕልና ያጎናጸፉ” ያሏቸው “የተወሰኑ” ልዕለ-ኃያላን፣ ለትዕዛዞቻቸው “የማይንበረከኩትን ለመቅጣት”፣ የተመድ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤትን እንደ መሣሪያ ይጠቀማሉ ሲሉ አቶ የማነ በኤክስ ባሰፈሩት መልክት ወንጅለዋል።
አቶ የማነ የአውሮፓ ኅብረትን የወነጀሉት መንግሥታቸው በኤርትራ ተፈጽመዋል የተባሉ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን ለመመርመር በተባበሩት መንግሥታት የሚሾሙ ባለሙያ ሥልጣን እንዲያበቃ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ በተደረገ ማግስት ነው።
DW Amharic
