የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር በኢራን ላይ ‘ቀድሞ የማጥቃት’ እርምጃ መውሰዱን ሲያስታውቅ በመላዋ አገሪቱ የአደጋ ጊዜ የማስጠንቀቂያ ደውል መሰማቱ ተዘገበ።
እስራኤል ጥቃቱን ተከትሎ በመላዋ አገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አውጃለች።
እርምጃው ከኢራን በኩል ሊፈጸም የሚችል ጥቃትን ቀድሞ ለመከላከል የተወሰደ መሆኑን ገልጾ፣ ይህንን ተከትሎ ከኢራን በኩል የአጸፋ የሚሳዔል ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል አስጠንቅቋል።
በተጨማሪም የእስራኤል መከላከያ ኃይል ‘ተደጋጋሚ የተኩስ አቁም ጥሰት በመፈጸሙ’ በጎረቤት ደቡባዊ ሊባኖስ ውስጥ በሚገኙ የሄዝቦላህ ጥቃት መፈጸሙንም አስታውቋል።
የቢቢሲ የኢራን ቋንቋ አገልግሎት ፋርስ ዜና ወኪል በመጥቀስ እንደዘገበው በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ማዕከላዊ ክፍል ውስጥ በርካታ ፍንዳታዎች መሰማታቸውን ዘግቧል።
የዜና ወኪሉ ቴህራን ውስጥ የሚገኙ ሁለት አካባቢዎች በተለይ ዒላማ መሆናቸውን እና በተጨማሪም ሦስት ፍንዳታዎችን የሚያሳዩ ሦስት ፎቶዎችንም አጋርቷል።

