እስራኤል የአሜሪካን የተኩስ አቁም ሃሳብ መቀበሏን አስታወቀች

Date:

የእስራኤል መንግሥት በዶናልድ ትራምፕ የቀረበውን የተኩስ አቁም ሃሳብ መቀበሉን ገለፀ።

ዛሬ ማለዳ ላይ ባወጣው መግለጫ “እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነቱ ከተጣሰ ጠንካራ ምላሽ ትሰጣለች” ብሏል።

የእስራኤል መንግሥት በኢራን ላይ ያደረሰው ጥቃት “ዓላማውን” ማሳካቱን በመግለጽ የተኩስ አቁም ሃሳብን ተቀብያለሁ ብሏል።

እስራኤል አክላም ኢራን በኒውክሌር ጦር መሳሪያ እና በባለስቲክ ሚሳኤሎች የደቀነችውን “ሁለት ፈጣን የኅልውና ስጋት” አስወግጃለሁ ብላለች።

በተጨማሪም እስራኤል “በወታደራዊ አመራር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

እንዲሁም በርካታ የኢራን መንግሥት ዒላማዎችን አውድሜያለሁ” ብላለች።

የእስራአል መንግሥት መግለጫ በመቀጠል የእስራኤልኃይሎች በመጨረሻውቀን በወሰዱት እርምጃ “በቴህራን ማዕከላዊ ክፍል በሚገኝ የመንግሥት ዒላማዎችን በመቶዎች የሚቆጠሩ የባሲጅ አባላትን” ማስወገዳቸውን ገልጿል።

የባሲጅ ታጣቂዎች የኢራን መንግሥት ተቃውሞን ለማፈን የሚጠቀምባቸው ሚሊሻዎች ናቸው።

መግለጫው አክሎም በዚሁ ጥቃት “ሌላ ከፍተኛ የኒውክሌር ሳይንቲስትን ተገድሏል” ብሏል።

“እስራኤልፕሬዝዳንት ትራምፕን እና አሜሪካን በመከላከያ ላደረጉት ድጋፍ እና የኢራንን የኒውክሌር ስጋት ለማስወገድ ላሳዩት ተሳትፎ ምስጋና አቅርበዋል” ሲል መግለጫው ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...