ኩባንያው በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ስራውን የጀመረ ሲሆን ወደ ሌሎች የሀገሪቱ ከተሞችም ለማስፋፋት እቅድ እንዳለው አስታውቋል።
ኩባንያው በኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ ለመጀመር የሁለት ዓመት ድርድር ማድረጉንና በሂደቱ ውስጥም የተለያዩ ተግዳሮቶች እንደገጠሙት ገልጿል።
በተለይም ዓለም አቀፍ የንግድ ልምዶችን እና የኢትዮጵያን የሕግ ማዕቀፍ ማጣጣም ትልቅ ፈተና እንደነበረበት አስታውቋል።
ግሪን ሞሽን ከኤክስፔዲያ እና ቡኪንግ.ኮም ከመሳሰሉ ዓለም አቀፍ የቦታ ማስያዣ መድረኮች ጋር የተዋሃደ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለአገር ውስጥና ለአለም አቀፍ ተጓዦች ምቹ አገልግሎት ለመስጠት በኢትዮጵያ ከሚገኘዉ ኤክሰለንስ መኪና ኪራይ ኩባንያ ጋር በሽርክና መስራቱን ገልጿል።
ኩባንያው በኢትዮጵያ ስራ በመጀመሩ የውጭ ምንዛሪ እንደሚያስገኝና ለአካባቢው ኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
Source: capitalethiopia
