የኔቶን በጀት በ400% ማሳደግ ይገባል ተባለ
የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ድርጅት (NATO) “እየጨመሩ መጥተዋል” ያላቸውን ስጋቶች ለመቀነስ የአየር እና የሚሳዔል አቅምን ማሳደግ እንደሚገባ ዋና ፀሐፊው ማርክ ሩቴ ተናግረዋል።
ሩቴ በለንደን ቻታም ሀውስ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ስጋቶች በተለየ መልኩ ከሩሲያ እና ቻይና እንደሚመነጩ ተናግረዋል።
ዋና ፀሐፊው፣ “ኔቶ በአንድ አመት የሚያመርተውን የመሳሪያ አቅም ሩሲያ በሶስት ወር እያመረተችው ነው” ሲሉ በንፅፅር አስረድተዋል።
ነገር ግን “እኛን ማጥቃት የሚፈልግ፣ ሩሲያም ትሁን ሌላ መዘዙ አስከፊ ነው” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
