በጋዛ የተደረጉ ጥናቶች እንዳመላከቱት ከ90 በመቶ በላይ በጋዛ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ወድመዋል ተብሏል፡፡
የጋዛን ነዋሪዎች ማንነትን የሚገልጹ እንደ ባህልና የእምንት ታዎችን እንዲሁም ትምህርት ቤቶችን በማጥፋት አለምአቀፉ ገለልተኛ የምርመራ ኮሚሽን እስራኤልን ተጠያቂ አድርጓል፡፡
በተባበሩት መንግስታት የአለምአቀፍ ገለልተኛ የምርመራ ኮሚሽን ይዞት በወጣዉ ሪፖርት እስራኤል የፍልስጤማዊያንን ማንነት ከምድር ለማጥፋት እንደ ትምህርት ቤቶችና የሃይማኖት ተቋማት ላይ የጥፋት ወንጀል እያደረገች ነዉ ብሏል፡፡
ከዚህ በፊት ኮሚሽኑ ባወጣዉ ሪፖርት እስራኤል በጋዛ ግጭት ወቅት የሴቶችን የጤና መጠበቂያ ተቋማትን ስልታዊ በሆነ መንገድ በማጥፋት ፍልስጤማውያን ላይ “የዘር ማጥፋት ድርጊቶችን” ፈጽማለች በማለቱ፤ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ሪፖርቶቹ አድሎአዊ እና ፀረ ሴማዊ ናቸው በማለት ወቅሰዋል፡፡
በዚህ ምክኒያት እስራኤል ከኮሚሺኑን እራሷን ማግለለዋን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታዉቋል፡፡
የኮሚሽኑ ሊቀመንበር የነበሩት የቀድሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ናቪ ፒሌይ “እስራኤል በጋዛ ውስጥ እያደረሰችዉ ያለዉ ጉዳት እየጨመረ መምጣቱን እያየን ነው” ሲሉም ተናግረዋል።
ኮሚሽኑ በትምህርት ተቋማት፤በሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ቦታዎች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶችን የመረመረ ሲሆን በምርመራዉም አለም አቀፍ ህጎች መጣሳቸዉን አረጋግጫለሁ ማለቱን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
