“ከትራምፕ ጋር አንተባበርም” ቺካጎ

Date:

የቺካጎ ከንቲባ የዶናልድ ትራምፕን ውሳኔ በመቃወም የከተማዋ ፖሊስ ከብሄራዊ ዘቡ ጋር እንዳይተባበር አዘዙ።

የፌደራሉን መንግስት ጣልቃ ገብነት አግባብነት የሌለው ነው ያሉት ከንቲባው መተባበር አያሻንም፤ በራሳችን መወጣት የምንችለውን ጉዳይ ብሄራዊ ዘብ ሀይል ማስፈር ትርጉም የለውም ብለዋል።

የቺካጎ ከንቲባ ብራንዶን ጆንሰን ትራምፕን የተቃወመ ትዕዛዝ ሰተዋል፤ ፊርማቸውንም አሳርፈዋል።

ፖሊስ ከየትኞቹም የፌደራል ሀይሎች ጋር ትብብር እንዳይኖረው የሚከለክለው ውሳኔ ምናልባትም በአሜሪካ ተጨማሪ አለመረጋጋትን እንዳይፈጥር ስጋት ጋርጧል።

ሪፐብሊካኑ ትራምፕ በሚቀጥሉት ቀናት ውስጥ ብሄራዊ ዘቡን ወደ ቺካጎ ሊልኩ እንደሚችሉ እየተነገረ ነው።

ዴሞክራቱ ከንቲባ ጆንሰን ደግሞ ይህን ውሳኔ መቃወማቸው እና አንተባበርም የሚል አቋም ላይ መድረሳቸው በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል ፖለቲካዊ እሰጥ አገባው እየበረታ መሄዱን የሚያሳይ ያደርገዋል።

ዶናልድ ትራምፕ በሎስ አንጀለስና ዋሽንግተን ዲሲ ብሄራዊ ዘብ አስፍረው ከተሞችን ተቆጣጥረዋል በሚልም በዴሞክራቶቹ እየተወቀሱ ነው።

ትራምፕ ዴሞክራት ከንቲባዎች በሚያስተዳድሯቸው ከተሞች ላይ ትኩረት አድርገዋል ቢባሉም ከተሞቹን ከወንጀል ነጻ ለማድረግ አማራጩ ይህ ነው ብለውታል።

ከተሞቹ እየሰሩ ያለውን ስራ ግምት ውስጥ ሳያስገባ እንዲሁም ስጋት በሌለበት አጋጣሚ ብሄራዊ ዘቡን ትራምፕ አሰማርተዋል ይላሉ ዴሞክራቶ ሲል ኤን ቢ ሲ ኢንዲያ ቱዴይን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...