ነሐሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም፣ (ሀገሬ ቴቪ)፤ ኦቪድ ሪል እስቴት ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ቅናሽ ተደርጎባቸዋል የተባሉ ቤቶችን የሚሸጥበትን ኤክስፖ አስጀምሯል።
ከዛሬ ነሐሴ 24 ጀምሮ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ቆይታ የሚያደርገው ይህ ኤክስፖ በአነስተኛ ቅድመ ክፍያ ቤቶች የሚሸጡበት መሆኑም ተነግሯል።
እስከ ሁለት ዓመት በሚደርስ ጊዜ ውስጥ የቤቶችን ግንባታ በማጠናቀቅ ለደንበኞች ለማስረከብ አቅደናል ያሉት የኦቪድ ሪል እስቴት ማርኬቲንግ ማናጀር መቅደስ ቀደመ፤ ለደንበኞች የረዥም ጊዜ የክፍያ አማራጭ መመቻቸቱን ጠቁመዋል።
ኤክስፖው ገርጂ በሚገኘው የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሳይት ግቢ ውስጥ እየተካሄደ ይገኛል።
