ዐዲስ ቸኮል ቀዶ ሕክምናውን አጠናቆ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛል!

Date:


የአሜሪካ ድምጽ፣ የድሬዳዋ ዘጋቢ ዐዲስ ቸኮል፣ የተደረገለት ቀዶ ሕክምና ተሳክቶ በጥሩ ኹኔታ ላይ ይገኛል።
ዐዲስ ቸኮል፣ ከቀዶ ሕክምናው በኋላ የንግግር እክል ሊያጋጥመው ይችላል በሚል የነበረው ፍርሃት ሙሉ ለሙሉ ተወግዷል። ከቀዶ ሕክምናው በኋላ በተደረገለት ክትትል የንግግር ብቃቱ፣ ቀድሞ ወደ ነበረው ጤናው መመለሱን አረጋገጠዋል።

ሰባት ሰዓት አካባቢ በፈጀ ቀዶ ሕክምናም፣ ዕጢው ሙሉ ለሙሉ ወጥቶለታል። በአኹኑ ሰዓት በሆስፒታሉ ውስጥ በማገገም ላይ ይገኛል።
“እግዚያብሔር ይመስገን ለዚኽ በቅቻለኹ” ያለው ዐዲስ፣ “ እኔን እዚኽ ለማድረስ የተረባረባችኹ በሙሉ እግዚያብሔር ብድራችኹን ይክፈላችኹ። ለእኔ እንደደረሳችኹልኝ። እግዚያብሔር ለእናንተም ይድረስላችኹ” ብሏል።

ዐዲስን ለማሳከም፣ የተረባረበው ሰው በቁጥርና በስም ተለይቶ የሚቀመጥ አይደለም። በኹሉም ነገር ከላይ እስከ ታች የተሳተፈው በሙሉ ድጋፉ ፍሬ አፍርቷልና፣ ኹላችሁንም እግዚያብሔር ይባርካችኹ። በደግ ይመልስላችኹ።


ጓደኞቹ እና የሞያ አጋሮቹ!

ከጋዜጠኞ ይትባረክ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...