ፍርድ ቤቱ በኢትዮጵያና በአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤቶች ሕንፃ ውዝግብ ላይ የእግድ ውሳኔ አስተላለፈ

Date:

በኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (ኢትዮጵያ ቻምበር) እና በአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) መካከል በሜክሲኮ አደባባይ በሚገኘው የንግድ ምክር ቤቶች ሕንፃ ላይ በቀረበው የይገባኛል ውዝግብ ላይ፣ የቂርቆስ ምድብ 1ኛ ፍ/ብሄር ችሎት የእግድ ዉሳኔ አስተላልፏል።

ፍርድ ቤቱ በዛሬው እለት በሰጠው ውሳኔ መሰረት፣ ኢትዮጵያ ቻምበር ቀደም ሲል ይዞ የነበረውን የቢሮ ክፍል በአስቸኳይ ለአዲስ ቻምበር እንዲያስረክብ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ ይህን ውሳኔ የሰጠው፣ ኢትዮጵያ ቻምበር ቀደም ሲል የፍርድ ቤቱን ብይን በመጣስ፣ አዲስ ቻምበር ይዟቸው የነበሩ ክፍሎችን በኃይል እንደያዘ አዲስ ቻምበር ባቀረበው አቤቱታ መሰረት ነው።

ፍርድ ቤቱ ህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ባሳለፈው ብይን፣ ተከሳሽ (ኢትዮጵያ ቻምበር) ሕንጻውን ለልማት ከማዋሉ በፊት ለአዲስ ቻምበር ምትክ ክፍሎችን አስቀድሞ ማዘጋጀትና ለፍርድ ቤቱ ማሳወቅ እንደነበረበት አመልክቶ ነበር።

የኢትዮጵያ ቻምበር ይህንን ትዕዛዝ በመጣስ የክፍሎቹን ቁልፎች ሰብሮ መግባቱ በአዲስ ቻምበር በኩል መገለጹን ተከትሎ፣ ፍርድ ቤቱ ኢትዮጵያ ቻምበር ክፍሎቹን በአስቸኳይ ለከሳሽ (አዲስ ቻምበር) እንዲያስረክብ በድጋሚ በጥብቅ አዟል።

Capital news

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...