የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ የዩክሬን የመጀመሪያዋ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዩሊያ ስቪሪደንኮ፣ የሀገሪቱን መንግሥት እንዲመሩ ሀሳብ ማቅረባቸው ተገለፀ።
ዩክሬን የአቀደችው ግብ ወደ ስኬት እንዲደርስ የአስፈፃሚ አካል ለውጥ ልታደርግ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል።
ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ በኤክስ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ከመጀመሪያዋ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማጎልበት፣ የሀገር ውስጥ የጦር መሣሪያዎችን ምርት ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መወያየታቸውን ገልፀዋል።
ዩሊያ ስቪሪደንኮ እኤአ በህዳር 2021 የመጀመሪያዋ የዩክሬን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የሆኑ ሲሆን፤ ከዚህ ሀላፊነታቸው በፊት የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
