በአንበሳ አውቶብስ ሲካሄድ የቆየው የሸገር ዳቦ ሽያጭ ሙሉ ለሙሉ መቆሙን የአዲስ አአባ ከተማ ንግድ ቢሮ ለመናኸሪያ ሬዲዮ አስታውቋል፡፡
በ2012 ዓ.ም 80 ሺህ ዳቦ ያመርታል ተብሎ ወደ ስራ ለገባው የሸገር ዳቦ ምርት መሸጫ ታስበው የተዘጋጁ የአንበሳ አውቶብሶች ሙሉ ለሙሉ ስራ ማቆማቸውን የአዲስ አአባ ከተማ ንግድ ቢሮ የቁጥጥር ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ስመኘው ተሾመ ተናግረዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ በወጣው የከተማ ስታንዳርድ ምክንያት ለሸገር ዳቦ መሸጫነት ይውሉ የነበሩ አንበሳ አውቶብሶች ከአገልግሎት እንደወጡ በመጥቀስ፣ አሁን ላይ ከተማውን በሚመጥኑ ስታንዳርድ ሱቆችና ልዩ ልዩ ማከፋፈያዎች ብቻ አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ሃላፊው ለጣቢያው አብራርተዋል።
የሸገር ዳቦ ሽያጭ በሁሉም ክፍለ ከተማ በዘመናዊ ሱቆች መቅረቡ እንደሚቀጥል የገለጹት አቶ ስመኘው፤ የከተማዋን ገፅታ የማይመጥኑ የንግድ ማዕከላትን የማፅዳቱ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
