የቡና ላኪዎች የመነሻ ካፒታል በ900 በመቶ እንዲጨምር ያድርጋል የተባለው ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ

Date:

የግብርና ሚኒስቴር የቡና ላኪዎች የብቃት ማረጋገጫ ለማግኘት የሚጠይቀውን ዝቅተኛ የመነሻ ካፒታል በግለሰብ ደረጃ በ900 በመቶ እንዲሁም ለአክሲዮን ማህበራትና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበራት ደግሞ በተመሳሳይ መልኩ ጭማሪ የተደረገበትን ረቂቅ መመሪያ አዉጥቷል።

በዚሁ ረቂቅ መሰረት፣ የግል የቡና ላኪዎች ከዚህ ቀደም ይጠበቅባቸው የነበረው አንድ ሚሊዮን ብር ዝቅተኛ ካፒታል ወደ 10 ሚሊዮን ብር እንዲያድግ ታቅዷል። በተጨማሪም፣ አመልካቾች የአንድ ዓመት የፋይናንስ እንቅስቃሴን የሚያሳይ በባንክ የተረጋገጠ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

በተመሳሳይ ሁኔታ፣ ለአክሲዮን ማህበራት እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበራት የሚፈለገው ዝቅተኛ የመነሻ ካፒታል ከ 1 ሚሊዮን 500 መቶ ሺህ ብር ወደ 15 ሚሊዮን ብር ከፍ እንዲል የቀረበ ሲሆን፣ ከማህበሩ መስራቾች መካከል ቢያንስ ሁለቱ ከፍተኛ ድርሻ ያላቸው አባላት የአንድ ዓመት የፋይናንስ እንቅስቃሴ የሚያሳይ የባንክ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል ይላል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...