የትራምፕና ዘለንስኪ ውይይት

Date:


የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ሊወያዩ መሆኑ ተሰምቷል። ዘለንስኪ ለዚሁ ውይይት ወደ በርሊን ያቀናሉ የተባለ ሲሆን ከትራምፕ ጋር ሰፋ ያለ የቪዲዮ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ትራምፕ ከዘለንስኪ ባሻገር ሌሎች የአውሮፓ ሀገራት መሪዎች ጋር በኦንላይን ውይይት ያደርጋሉም ተብሏል።

ውይይቱ በዋነኝነት ትራምፕ በመጪው አርብ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ሲገናኙ የዩክሬንን ፍላጎት ያማከለ ስምምነት እንዲያደርጉ ለመምከር መሆኑም ተሰምቷል።

የጀርመኑ ቻንስለር ፍሬድሪክ ሜርዝ ለዚሁ የቪድዮ ስብሰባ ዘለንስኪን ጨምሮ እንግሊዝ ፤ፈረንሳይ፤ የአውሮፓ ህብረት አመራሮችን ወደ በርሊን ጠርተዋልም ተብሏል።

ትራምፕ ፑቲንን በመጪው አርብ በአላስካ ከማግኘታቸው አስቀድሞ የሚደረገው ይህ የቪድ ስብሰባ ላይ የትርምፕ ምክትል ጄዲ ቫንስ ተሳታፊ ይናሉ ተብሏል።

የመጪው አርብ የዶናልድ ትራምፕና የፑቲን በአካል መገናኘት የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜም ያርገዋል።በዚህም ኬቭ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ መግባቷ ተሰምቷል።

ዘገባው የፍራንስ 24 ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...