የትራምፕ ታሪፍ የአሜሪካ አምራቾችን እየጎዳ ነው

Date:

የአሜሪካን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማነቃቃት ታስበው በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የተጣሉት ታሪፎች፣ በተቃራኒው ዘርፉን እየጎዱት እንደሆነ እየታየ ነው።

መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ የአሜሪካ አምራቾች ከ100,000 በላይ ስራዎችን አጥተዋል።

ከውጭ በሚገቡ ምርቶችና መለዋወጫዎች ላይ የታከለው ከፍተኛ ወጪ ኩባንያዎች የዋጋ ጭማሪ እንዲያደርጉ ወይም ሰራተኞችን እንዲቀንሱ አስገድዷቸዋል።

ዋይት ሃውስ የትራምፕ ፖሊሲዎች ውሎ አድሮ ውጤት እንደሚያመጡ ቢገልጽም፥ በቅርቡ የታየው የፋብሪካዎች እድገት ግን በአብዛኛው ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ፖሊሲዎች ጋር የተያያዘ ነው።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “የአሜሪካ ፋብሪካዎችን ይረዳሉ” ያሏቸው ታሪፎች በተግባር ግን ብዙዎቹን እያዳከሙ እንደሆነ የሚያሳዩ መረጃዎች አሉ።

ከውጭ የሚገቡ እቃዎችና መለዋወጫዎች ዋጋ እንዲጨምር በማድረጉ በአሜሪካ ውስጥ ፋብሪካዎችን የማንቀሳቀስ ወጪ እንዲንር አድርጓል።

ብዙ አምራቾች የታሪፉን ወጪ ለመሸፈን በምርቶቻቸው ላይ የዋጋ ጭማሪ ለማድረግ ተገደዋል።

በሌሎች ሁኔታዎች ደግሞ ወጪን ለመቆጠብና የታሪፍ ጫናን ለመቋቋም ሲባል ስራዎችን መቀነስ የግድ ሆኗል።

ባለፈው አንድ ዓመት የአሜሪካ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ወደ 100,000 የሚጠጉ ስራዎችን ቀንሷል። ይህም ፕሬዝዳንት ትራምፕ “ታሪፎቹ ስራን ወደ አሜሪካ ይመልሳሉ” ካሉት ተስፋ ተቃራኒ ነው።

ዋይት ሃውስ በአሁኑ ወቅት የበርካታ አዳዲስ ፋብሪካዎች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንና ይህም ወደፊት ለተጨማሪ ስራዎች ዕድል እንደሚፈጥር ይከራከራል።

ሆኖም እነዚህ የግንባታ ፕሮጀክቶች በአብዛኛው የተጀመሩት ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የሴሚኮንዳክተር እና የአረንጓዴ ቴክኖሎጂ ምርትን ለማበረታታት በደነገጓቸው ህጎች አማካኝነት ነው።

ስለዚህ ታሪፎቹ እስካሁን አዎንታዊ ተፅዕኖ እያሳደሩ መሆኑን የሚያሳይ በቂ ማስረጃ የለም ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...