“የትግራይ ሕዝብ ሀገሩን ከሚወጉት ጋር ተሰልፎ የመዋጋት ጥቁር ታሪክ የለውም”

Date:

  • ወይዘሮ ኬርያ ኢብራሂም

የትግራይ ሕዝብ ሀገሩን ከሚወጉት ጋር ተሰልፎ የመዋጋት ጥቁር ታሪክ የለውም ሲሉ የቀድሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬርያ ኢብራሂም ገለጹ፡፡

የቀድሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬርያ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የሕወሓት ቡድን ግን የተሰለፈው ከትግራይ ሕዝብና ከሀገሪቱ ጠላት ጋር ነው።
የትግራይ ሕዝብ ሀገሩን የሚወድ እንጅ ከሕዝብና ከሀገሩ ጋር ተቃራኒ ሆኖ የሚሰለፍበት ምንም ዓይነት ሁኔታ የለም፤ እንደዚህ ዓይነት ታሪክም የለውም ብለዋል።

እንደ ወይዘሮ ኬርያ ገለጻ፤ የትግራይ ሕዝብና የትግራይ ምድር የጦር ሜዳ እንዳይሆን ህዝቡ ሊጠነቀቅ ይባል፡፡

ይህ እንዳይከሰት አሰላለፋችንን ማስተካከል እና ከጥፋት ኃይሎች በተቃራኒ መቆም አለብን ሲሉ መክረዋል።

ለትግራይ ሕዝብ ሲባል የጦርነት በር መዘጋት አለበት ያሉት ወይዘሮ ኬርያ፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ የትግራይ ተወላጆች ለሰላም ግፊት ማድረግ  እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የትግራይ ሕዝብ ጥያቄዎች መመለስ የሚቻለው ከፌዴራል መንግሥት ጎን በመሰለፍ በሰላማዊ እና በዲሞክራሲያዊ መንገድ እንጅ በጦርነት አይፈታም ሲሉም  አስረድተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...