ነጭ ናፍጣ በሊትር 163.09 ብር ገብቷል። ቤንዚንም በሊትር 142.41 ብር ሆኗል።
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል።
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ደብዳቤ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሰረት በማድረግ ከመጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሬ መደረጉን ያስረዳል።
በደብዳቤው በተገለጸው መሰረት በሊትር፦
- ነጭ ናፍጣ 163.09 ብር
- ቤንዚን 142.41 ብር
- ኬሮሲን 151.39 ብር - ቀላል ጥቁር ናፍጣ 163.98 ብር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 160.68 ብር
- የአውሮፕላን ነዳጅ 150.48 ብር ሆኗል።
