የኋይት ሃውስ ቃለ አቀባይ ስቴቨን ቼኡንግ ዶናልድ ትራምፕ የኖቤል የሰላም ሽልማትን አለማሸነፋቸውን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት ኮሚቴው ከሰላም በላይ ፖለቲካን ማስበለጡን አሳይቷል ብለዋል።
ቃለ አቀባዩ ” ትራምፕ የሰብዓዊነት ማዕከል ናቸው” በማለት ሌሎች ሊሞክሩ የማይደፍሩትን ነገር አሳክተዋል ሲሉ ገልፀዋል።
ትራምፕ በተደጋጋሚ ላቆምኳቸው ጦርነቶች የሰላም ሽልማት አልተሰጠኝም ሲሉ ዘንድሮ በተለይ የእስራኤል እና ኢራንን ጦርነት በማስቆም እንደዚሁም ደግሞ ከሰሞኑ በጋዛ ለተፈፀመው የሰላም ስምምነት በነበራቸው ሚና ሽልማቱን ይገባኛል ሲሉ በተደጋጋሚ በግልጽ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ ኢትዮጵያ እና ግብፅ ያልተዋጉትን ጦርነት ጨምሮ የሰርቢያና ኮሶቮ፣ የአርሜኒያ እና አዘርባጃን እንደዚሁም የህንድ እና ፓኪስታንን ግጭቶች አስቁሜያለሁ ብለው መናገራቸው ይታወሳል።
ዘገባው የአልጄዚራ ነው
