የአሜሪካ ዛቻ እስከቀጠለ ድረስ ድርድር እንደማይጀመር የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናገሩ

Date:

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ከኢራን ጋር ስምምነት ላይ የማይደረስ ከሆነ የተጀመረውን “ሥራ እንደሚያጠናቅቁ” መናገራቸውን ተከትሎ፤ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዛቻ እስከቀጠለ ድረስ ድርድር እንደማይጀመር ተናገሩ።

የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ በጄኔቫ የመጀመሪያ ዙር ንግግር ያደረጉት ዋሽንግተን እና ቴህራን፤ የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ቀብር እስከሚጠናቀቅ ድረስ ድርድሩን መግታታቸውን ትራምፕ ገልጸው ነበር።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ሰኞ ምሽት በዋይት ሐውስ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ “ስምምነት ላይ እንደርሳለን ወይም ሥራውን እናጠናቅቃለን። ሥራውን መጨረስ አስቸጋሪ አይሆንም” ሲሉ ተናግረዋል።

“በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ እናሸንፋለን” ያሉት ትራምፕ፤ “የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቻቸውን መምታት እንችላለን…እነርሱም ያውቁታል” ብለዋል።

ለዚህ የትራምፕ ንግግር ምላሽ ሰጡት ኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በበኩላቸው፤ ቴህራን ላይ የሚሰነዘረው “ዛቻ እስከቀጠለ ድረስ የመጨረሻ ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚደረገው ድርድር እንደማይጀምር” ገልጸዋል።

ሚኒስትሩ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፤ ከአሜሪካ ጋር የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነትን አንቀጽ 13ን ጠቅሰው “ግልጽ” ነው ብለዋል።

ሚኒስትሩ የጠቀሱት አንቀጽ በስምምነቱ ላይ የሰፈሩ ጉዳዮች ተግባራዊ እስካልሆኑ ድረስ ሁለቱ አገራት ለመጨረሻ ስምምነት የሚደረግን ድርድር እንደማይጀምሩ የሚገልጽ ነው።

በስምምነቱ ድንጋጌዎች አንዱ ሁለቱም አገራት አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ ኃይል እንዳይጠቀሙ ወይም እንዳይዝቱ ያዝዛል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አራግቺ የአያቶላህ አሊ ኻሜኒን የቀብር ሥነ ሥርዓት የሚያሳዩ ምሥሎችን ከፅሑፉ ጋር ለጥፈዋል። “በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኩሩ ኢራናውያን በአንድነት ታላቁን አያቶላህ ኻሜኒን እና አሻራቸውን ለማግበር ወጥተዋል” ሲሉ ጽፈዋል። አክለውም “እነርሱም ሆነ ደፋሩ ጦር ኃይላችን በማንኛውም ዛቻ አይነኩም” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ከፖለቲካ ራሳቸውን አገለሉ

ላለፉት 5 አስቸጋሪና ፈታኝ ዓመታት (ከ2014 እስከ 2018 ዓ.ም)...

ንባብ ለሕይወት  እየመጣ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

“ወጣቱን በጉልበት እያፈሱ ወደ ጦርነት እየነዱት ነው!”

"ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት በትግራይ፦ የመገናኛ ብዙኃን እና የማኅበረሰብ አንቂዎች...