የአፍሪካ ኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር በግል ዘርፍ ሊመራ እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ

Date:

በአፍሪካ ልማት ባንክ ቡድን የ2026 ዓመታዊ ስብሰባ ጎን ለጎን በብራዛቪል የተገናኙት የልማት ፋይናንስ መሪዎች፣ ሚኒስትሮች እና ስራ ፈጣሪዎች፤ የግል ኢንተርፕራይዞች እና የውስጥ ቀጣናዊ ንግድ ለአፍሪካ ትራንስፎርሜሽን ዋና ሞተሮች መሆናቸውን ገልጸዋል።

በባንኩ ቡድን የተደራጀው የዚህ የግል ዘርፍ መድረክ የተካሄደው “የኢኮኖሚ ኮሪደሮችን በማልማት ረገድ የግል ኢንተርፕራይዞች ሚና እና ተግዳሮቶች፣ እንዲሁም በድንበር ተሻጋሪ የእሴት ሰንሰለቶች ኢንዱስትሪላይዜሽን እና በውስጥ ቀጣናዊ ንግድ የአፍሪካ ኢኮኖሚዎች መዋቅራዊ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል ነው።

በአፍሪካ በማደግ ላይ ባሉ ኢኮኖሚዎች ውስጥ የግል ዘርፉ ከ80 በመቶ በላይ የመንግስትን ገቢ እና ከ90 በመቶ በላይ የሥራ ዕድል የሚፈጥር ሲሆን፤ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ደግሞ ከጠቅላላው የግል ድርጅቶች ውስጥ 90 በመቶውን ይሸፍናሉ።

ሆኖም ግን፣ በአብዛኛው በፋይናንስ እጥረት ሳቢያ ወደ ትላልቅ ኢንተርፕራይዞች ማደግ የቻሉት በጣም ጥቂቶቹ ብቻ መሆናቸው ለመረዳት ተችሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...